የመስሪያ ቦታዎች ልማትና አስተዳደር ኤጀንሲ በቦ...

image description
- ክስተቶች Uncategorized    0

የመስሪያ ቦታዎች ልማትና አስተዳደር ኤጀንሲ በቦሌ ለሚ ኢንዱስትሪ ፓርክ እና ሾላ የተባበሩት አምራች ማህበር ላይ ጉብኝት አካሂዷል።

በጉብኝቱም የኤጀንሲው የስራ ኃላፊዎችና ባለሙያዎች፣ የክ/ከተማ የመዋቅሩ ጽ/ቤት ኃላፊዎችና አስተባባሪዎች እና የመስሪያ ቦታዎች ግቢ ኮሚቴ ሰብሳቢዎች ተሳትፈዋል።
 
ጉብኝቱ በዋናነት በመስሪያ ቦታዎች ተረፈ ምርት አጠቃቀም፣ በገበያ ትስስር፣ በክላስተር ፅንሰ-ሀሳብ እና በመስሪያ ቦታዎች ምቹነት ላይ ያተኮረ ነው።
 
በጉብኝቱ ወቅት ንግግር ያደረጉት የኤጀንሲው ም/ዳይሬክተርና የመስሪያ ቦታ ልማትና ማስተላለፍ ዘርፍ ኃላፊ ወ/ሮ ሰብለወርቅ ታደሰ የጉብኝቱ ዋና አላማ የተሻሉ ተሞክሮዎችን በመውሰድ በሌሎች የመስሪያ ቦታዎችና በቀጣይም በሚገነቡ የመስሪያ ቦታዎች ላይ ለመተግበር እንደሆነ ገልፀዋል።
 
የኤጀንሲው ዋና አላማ የመስሪያ ቦታዎችን ማስገንባትና ማስተላለፍ እንደሆነ የገለፁት ወ/ሮ ሰብለወርቅ በጉብኝቱ የተሳተፉ አካላት ያገኙትን ምርጥ ተሞክሮ በሌሎች መስሪያ ቦታዎች ላይ መተግበር እንደሚገባቸው አሳስበዋል።
 
ወ/ሮ ሰብለወርቅ አክለውም ጉብኝቱ በቀጣይ ተገንብተው የሚተላፉ መስሪያ ቦታዎች ምቹ ለማድረግ እንደሚያስችላቸው ገልፀዋል።


Comments

ምንም አልተገኘም.

አስተያየቶችዎን ይተዉት.